10. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “አሁን እነሣለሁ፤አሁን ከፍ ከፍ እላለሁ፤አሁን እከብራለሁ።
11. ገለባን ፀነሳችሁ፤እብቅንም ወለዳችሁ፤እስትንፋሳችሁም የሚበላችሁ እሳት ነው።
12. ሕዝቦች ኖራ እንደሚወጣው ድንጋይ ይቃጠላሉ፤እንደ እሾኽ ቍጥቋጦ በእሳት ይጋያሉ።”
13. እናንት በሩቅ ያላችሁ ያደረግሁትን ስሙ፤እናንት በቅርብ ያላችሁ ኀይሌን ዕወቁ!
14. በጽዮን ያሉ ኀጢአተኞች ደነገጡ፤አምላክ የሌላቸውም ፍርሀት ይዞአቸው፣“ከእኛ መካከል ከሚባላ እሳት ጋር ማን መኖር ይችላል፣ከዘላለም እሳትስ ጋር ማን መኖር ይችላል?” አሉ።