ኤርምያስ 22:15-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. “በዝግባ ዕንጨት ብዛት፣የነገሥህ ይመስልሃልን?አባትህስ ፍትሕንና ጽድቅን በማድረጉ፣የሚበላውና የሚጠጣው ጐድሎት ነበርን?እነሆ፣ ሁሉም መልካም ሆነለት።

16. የድኾችንና የችግረኞችን ፍትሕ አላጓደለም፤ስለዚህም ሁሉ መልካም ሆነለት።እኔን ማወቅ ማለት ይህ አይደለምን?”ይላል እግዚአብሔር።

17. “የአንተ ዐይንና ልብ ያረፉት ግን፣አጭበርብሮ ጥቅምን በማግኘት፣የንጹሑን ደም በማፍሰስ፣ጭቈናንና ግፍን በመሥራት ላይ ብቻ ነው።

18. ስለዚህ እግዚአብሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ኢዮአቄም እንዲህ ይላል፤“ ‘ዋይ ወንድሜ! ዋይ፣ እኅቴን!’ብለው አያለቅሱለትም።‘ዋይ፣ ጌታዬን! ዋይ፣ ለግርማዊነቱ!’ብለውም አያለቅሱለትም።

19. አህያ እንደሚቀበር ይቀበራል፤ከኢየሩሳሌም በሮች ውጪ፤ተጐትቶ ይጣላል።

20. “ሊባኖስ ላይ ወጥተሽ ጩኺ፤ድምፅሽን በባሳን አሰሚ፤በዓባሪም ሆነሽ ጩኺ፤ወዳጆችሽ ሁሉ ወድመዋልና።

21. ተመችቶሽ በነበረ ጊዜ አስጠነቀቅሁሽ፤አንቺ ግን፣ ‘አልሰማም’ አልሽ፤ከትንሽነትሽ ጀምሮ መንገድሽ ይኸው ነበር፤ቃሌንም አልሰማሽም።

ኤርምያስ 22