20. ድንኳኔ ፈርሶአል፤ገመዶቹም ሁሉ ተበጣጥሰዋል፤ልጆቼ ጥለውኝ ሄደዋል፤ ከእንግዲህም አይመለሱም፤ድንኳኔን ለመትከል፣መጋረጃዬንም ለመዘርጋት ማንም የቀረ የለም።
21. እረኞቹ አእምሮ የላቸውም፤ እግዚአብሔርን አይጠይቁም፤ስለዚህ አልተከናወነላቸውም፤መንጎቻቸውም ሁሉ ተበታትነዋል።
22. መርዶ ስሙ! እነሆ፤ ከሰሜን ምድር፣ታላቅ ሽብር እየመጣ ነው፤የይሁዳን ከተሞች ባድማ፣የቀበሮዎችም መናኸሪያ ያደርጋል።
23. እግዚአብሔር ሆይ፤ የሰው ሕይወት በራሱ እጅ እንዳልሆነች፣አካሄዱንም በራሱ አቃንቶ ሊመራእንደማይችል ዐውቃለሁ።
24. እግዚአብሔር ሆይ፤ ቅጣኝ፤ ብቻ በመጠኑ ይሁንልኝ፤ፈጽሞ እንዳልጠፋ፣በቍጣህ አትምጣብኝ።
25. ያዕቆብን አሟጠው ስለበሉት፣ፈጽመው ስለዋጡት፣መኖሪያውንም ወና ስላደረጉ፣በማያውቁህ ሕዝቦች፣ስምህንም በማይጠሩ ወገኖች ላይ፣ቍጣህን አፍስስ።