16. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“መንታ መንገድ ላይ ቁሙ፣ ተመልከቱም፤መልካሟን፣ የጥንቷን መንገድ ጠይቁ፤በእርሷም ላይ ሂዱ።ለነፍሳችሁ ዕረፍት ታገኛላችሁ፤እናንተ ግን፣ ‘በእርሷ አንሄድም’ አላችሁ።
17. ጠባቂዎችን አቆምሁላችሁ፤‘የመለከትንም ድምፅ ስሙ’ አልኋችሁ፤እናንተ ግን፣ ‘አንሰማም’ አላችሁ።
18. እንግዲህ ሕዝቦች ሆይ ስሙ፤እናንተም ምስክሮች ምንእንደሚገጥማቸው አስተውሉ።
19. ምድር ሆይ፤ ስሚ፤ቃሌን ስላላደመጡ፣ሕጌንም ስለናቁ፣በዚህ ሕዝብ ላይ የሐሳባቸውን ውጤት፣ጥፋትን አመጣባቸዋለሁ።
20. ዕጣን ከሳባ ምድር፣ጣፋጩ ቅመም ከሩቅ አገር ቢመጣ ምን ይጠቅመኛል?የሚቃጠል መሥዋዕታችሁን አልቀበልም፤ሌላውም መሥዋዕታችሁ ደስ አያሰኙኝም፤
21. ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤በዚህ ሕዝብ ፊት መሰናክልን አስቀምጣለሁ፤አባቶችና ወንዶች ልጆች በአንድነት ይደናቀፉበታል፤ጎረቤቶችና ባልንጀሮችም ይጠፋሉ።”
22. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ ሰራዊት፣ከሰሜን ምድር እየመጣ ነው፤ከምድር ዳርቻም፣ታላቅ ሕዝብ እየተነሣሣ ነው።