18. እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤“በዚህች ምድር የሚኖሩትን፣አሁን ወደ ውጪ እወነጭፋቸዋለሁ፤ጒዳቱ እንዲሰማቸው፣መከራ አመጣባቸዋለሁ፤”
19. ስለ ስብራቴ ወዮልኝ፤ቍስሌም የማይድን ነው፤ግን ለራሴ እንዲህ አልሁት፤“ይህ የኔው ሕመም ነው ልሸከመውም ይገባኛል።”
20. ድንኳኔ ፈርሶአል፤ገመዶቹም ሁሉ ተበጣጥሰዋል፤ልጆቼ ጥለውኝ ሄደዋል፤ ከእንግዲህም አይመለሱም፤ድንኳኔን ለመትከል፣መጋረጃዬንም ለመዘርጋት ማንም የቀረ የለም።
21. እረኞቹ አእምሮ የላቸውም፤ እግዚአብሔርን አይጠይቁም፤ስለዚህ አልተከናወነላቸውም፤መንጎቻቸውም ሁሉ ተበታትነዋል።
22. መርዶ ስሙ! እነሆ፤ ከሰሜን ምድር፣ታላቅ ሽብር እየመጣ ነው፤የይሁዳን ከተሞች ባድማ፣የቀበሮዎችም መናኸሪያ ያደርጋል።
23. እግዚአብሔር ሆይ፤ የሰው ሕይወት በራሱ እጅ እንዳልሆነች፣አካሄዱንም በራሱ አቃንቶ ሊመራእንደማይችል ዐውቃለሁ።