9. የጥንቱን፣ የቀደመውን ነገር አስታውሱ፤እኔ አምላክ ነኝ፤ ከእኔም በቀር ሌላ የለም፤እኔ አምላክ ነኝ፤ እንደ እኔ ያለ የለም።
10. የመጨረሻውን ከመጀመሪያው፣ገና የሚመጣውንም ከጥንቱ ተናግሬአለሁ፤‘ዐላማዬ የጸና ነው፤ደስ የሚያሰኘኝንም ሁሉ አደርጋለሁ’ እላለሁ።
11. ከምሥራቅ ነጣቂ አሞራ፣ከሩቅ ምድር ዐላማዬን የሚፈጽም ሰው እጠራለሁ።የተናገርሁትን አደርጋለሁ፤ያቀድሁትን እፈጽማለሁ።
12. እናንት እልኸኞች፣ከጽድቅም የራቃችሁ ስሙኝ።
13. ጽድቄን እያመጣሁ ነው፤ሩቅም አይደለም፤ማዳኔም አይዘገይም።ለጽዮን ድነትን፣ለእስራኤል ክብሬን አጐናጽፋለሁ።