12. ስለዚህ ዕቃውን የሚገለብጡ ሰዎችን፤የምልክበት ጊዜ ይመጣል፤”ይላል እግዚአብሔር።“እነርሱም ይደፉታል፤ዕቃውን ባዶ ያስቀራሉ፤ማንቆርቆሪያዎቹንም ይሰባብራሉ።
13. የእስራኤል ቤት፤በቤቴል ታምኖ እንዳፈረ ሁሉ፣ሞዓብም በካሞሽ ያፍራል።
14. “እናንተ፣ ‘እኛ ተዋጊዎች ነን፤በጦርነትም ብርቱ ነን’ ልትሉ እንዴት ቻላችሁ?
15. ሞዓብ ትጠፋለች፤ ከተሞቿም ይወረራሉ፤ምርጥ ወጣቶቿም ወደ መታረድ ይወርዳሉ፤”ይላል ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የሆነው ንጉሥ፤
16. “የሞዓብ ውድቀት ተቃርቦአል፤ጥፋቱም ፈጥኖ ይመጣበታል።
17. በዙሪያው የምትኖሩ ሁሉ፤ዝናውን የምታውቁ ሁሉ አልቅሱለት፤‘ብርቱው ከዘራ፣የከበረው በትር እንዴት ሊሰበር ቻለ’ በሉ።
18. “ሞዓብን የሚያጠፋ፣በአንቺ ላይ ይመጣልና፤የተመሸጉ ከተሞችሽንም ያጠፋልና፤አንቺ የዲቦን ሴት ልጅ ሆይ፣ከክብርሽ ውረጂ፣በደረቅም መሬት ተቀመጪ።
19. አንቺ በአሮዔር የምትኖሪ ሆይ፤በመንገድ አጠገብ ቆመሽ ተመልከቺ፤የሚሸሸውን ወንድ፣ የምታመልጠውንም ሴት፣ምን ተፈጠረ?’ ብለሽ ጠይቂ።
20. ሞዓብ በመፍረሱ ተዋርዷል፤ዋይ በሉ፤ ጩኹ፤የሞዓብን መደምሰስ፣በአርኖን አጠገብ አስታውቁ።
21. ፍርድ በዐምባው ምድር፦በሖሎን፣ በያሳና በሜፍዓት ላይ፣
22. በዲቦን፣ በናባውና በቤት ዲብላታይም ላይ፣
23. በቂርያታይም፣ በቤት ጋሙልና በቤትምዖን ላይ፣
24. በቂርዮትና በባሶራ ላይ፤በሩቅና በቅርብ፣ ባሉት በሞዓብ ከተሞች ሁሉ ላይ መጥቶአል።
25. የሞዓብ ቀንድ ተቈርጦአል፤እጁም ተሰባብሮአል፤”ይላል እግዚአብሔር።