ኤርምያስ 4:21-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

21. እስከ መቼ የጦርነት ዐርማ እመለከታለሁ?እስከ መቼስ የመለከት ድምፅ እሰማለሁ?

22. “ሕዝቤ ተላሎች ናቸው፤እኔን አያውቁኝም።ማስተዋል የጐደላቸው፣መረዳትም የማይችሉ ልጆች ናቸው።ክፋትን ለማድረግ ጥበበኞች፤መልካም መሥራት ግን የማያውቁ።”

23. ምድርን ተመለከትሁ፤እነሆ ቅርጽ የለሽና ባዶ ነበረች፤ሰማያትንም አየሁ፣ብርሃናቸው ጠፍቶአል።

24. ተራሮችን ተመለከትሁ፣እነሆ ይንቀጠቀጡ ነበር፤ኰረብቶችም ሁሉ ተናጡ።

25. አየሁ፤ ሰው አልነበረም፤የሰማይ ወፎች ሁሉ በረው ጠፍተዋል።

26. ተመለከትሁ፤ እነሆም፣ ፍሬያማው ምድር በረሓ ሆነ፤ከተሞቹ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት፣ከብርቱ ቍጣው የተነሣ ፈራረሱ።

27. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ምድር ሁሉ ባድማ ትሆናለች፤ነገር ግን ፈጽሜ አላጠፋትም።

ኤርምያስ 4