ኤርምያስ 30:10-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. “ ‘ስለዚህ፤ አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፤ አትፍራ፤እስራኤል ሆይ፤ አትደንግጥ፤’ይላል እግዚአብሔር፤‘አንተን ከሩቅ አገር፣ዘርህንም ከተማረኩበት ምድር እታደጋለሁ፤ያዕቆብ ተመልሶ በሰላምና በርጋታ ይቀመጣል፣የሚያስፈራውም አይኖርም።

11. እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፤ አድንሃለሁም፣ይላል እግዚአብሔር፤‘በአሕዛብ መካከል በትኜሃለሁ፤እነዚህን አሕዛብ ሁሉ ፈጽሜ አጠፋለሁ፤አንተን ግን ሙሉ በሙሉ አላጠፋህም፤በመጠኑ እቀጣሃለሁ እንጂ፣ያለ ቅጣት አልተውህም።

12. “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ ‘ስብራትህ የማይጠገን፣ቍስልህም የማይድን ነው።

13. የሚሟገትልህ ሰው የለም፤ለቍስልህ መድኃኒት አይኖርም፤ፈውስም አታገኝም።

14. ወዳጆችህ ሁሉ ረስተውሃል፤ስለ አንተም ግድ የላቸውም።ጠላት እንደሚመታ መታሁህ፤እንደ ጨካኝም ቀጣሁህ፤በደልህ ታላቅ፣ኀጢአትህም ብዙ ነውና።

15. ፈውስ ለማይገኝለት ሕመምህ፣ስለቍስልህ ለምን ትጮኻለህ?በደልህ ታላቅ፣ ኀጢአትህም ብዙ ስለ ሆነ፣እነዚህን ሁሉ አድርጌብሃለሁና።

16. “ ‘ነገር ግን አሟጠው የበሉህ ሁሉ እንደዚያው ይበላሉ፤ጠላቶችህ ሁሉ ለምርኮ ዐልፈው ይሰጣሉ፤የሚዘርፉህ ይዘረፋሉ፤የሚበዘብዙህም ሁሉ ይበዘበዛሉ።

17. አንተን ግን መልሼ ጤነኛ አደርግሃለሁ፤ቍስልህንም እፈውሳለሁ፤’ይላል እግዚአብሔር።“ ‘የተናቀች፣ማንም የማይፈልጋት ጽዮን” ብለውሃልና።’

ኤርምያስ 30