ኤርምያስ 22:8-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. “ከተለያየ አገር የመጡ ሕዝቦች በዚህች ከተማ በኩል ሲያልፉ፣ ‘እግዚአብሔር በዚህች ታላቅ ከተማ ላይ ለምን እንዲህ አደረገ?’ እያሉ እርስ በርስ ይነጋገራሉ፤

9. ከዚያም፣ ‘የአምላካቸውን የእግዚአብሔርን ኪዳን ትተው ሌሎችን አማልክት ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው’ ይላሉ።”

10. ከእንግዲህ ስለማይመለስ፣የተወለደባትንም ምድር ዳግመኛ ስለማያይ፣ለተማረከው ንጉሥ አምርራችሁ አልቅሱ እንጂ፣ቀድሞ ለሞተው አታልቅሱ፤ አትዘኑም።

11. በአባቱ ምትክ በይሁዳ ላይ ስለ ነገሠው፣ ከዚህ ስፍራ በምርኮ ስለ ተወሰደው፣ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ሰሎ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ “ከእንግዲህ አይመለስም፤

12. ተማርኮ በሄደበት አገር ይሞታል እንጂ ይህቺን ምድር ዳግመኛ አያይም።”

13. “ቤተ መንግሥቱን በግፍ ለሚሠራ፣ሰገነቱንም ፍትሕ በማዛባት ለሚገነባ፣ወገኑን በነጻ ለሚያሠራ፣የድካሙንም ዋጋ ለማይከፍለው፣

14. ‘ባለ ትልልቅ ሰገነት፣ሰፊ ቤተ መንግሥት ለራሴ እሠራለሁ’ ለሚል ወዮለት!ሰፋፊ መስኮቶችን ያበጅለታል፤በዝግባ እንጨት ያስጌጠዋል፤ቀይ ቀለምም ይቀባዋል።

ኤርምያስ 22