10. የፈራረሰችው ከተማ ባድማ ሆነች፤የየቤቱም መግቢያ ተዘጋ።
11. በየአደባባዩ የወይን ጠጅ ያለህ እያሉ ይጮኻሉ፤ደስታው ሁሉ ወደ ሐዘን ይለወጣል፤ሐሤቱም ሁሉ ከምድር ገጽ ጠፍቶአል።
12. ከተማዪቱ ፈጽማ ፈርሳለች፤በሮቿም ደቀው ወድቀዋል።
13. የወይራ ዛፍ ሲመታ፣የወይንም ዘለላ ሲቈረጥ ቃርሚያ እንደሚቀር ሁሉ፣በምድሪቱ ላይ፣በሕዝቦችም ላይ እንዲሁ ይሆናል።
14. ድምፃቸውን ከፍ ያደርጋሉ፤ በደስታም ይጮኻሉ፤ከምዕራብም የእግዚአብሔርን ክብር ያስተጋባሉ።
15. ስለዚህ በምሥራቅ ለእግዚአብሔር ክብር ስጡ፤ከባሕር ደሴቶችም፣የእስራኤልን አምላክ፣ የእግዚአብሔርን ስም ከፍ ከፍ አድርጉ።
16. “ለጻድቁ ክብር ይሁን” የሚል ዝማሬ፣ከምድር ዳርቻ ሰማን፤እኔ ግን፣ “ከሳሁ፤ መነመንሁ፤ወዮልኝ!ከዳተኞች አሳልፈው ሰጡ፤ከዳተኞች በክሕደታቸው አሳልፈው ሰጡ” አልሁ።
17. በምድር የምትኖር ሕዝብ ሆይ፤ሽብር፣ ጒድጓድና ወጥመድ ይጠብቁሃል።
18. ከሽብር ድምፅ የሚሸሽ፣ወደ ጒድጓድ ይገባል፤ከጒድጓድ የወጣም፣በወጥመድ ይያዛል።የሰማይ መስኮቶች ተከፍተዋልና፤የምድርም መሠረት ተናወጠ።
19. ምድር ተከፈለች፤ምድር ተሰነጠቀች፤ምድር ፈጽማ ተናወጠች።
20. ምድር እንደ ሰካራም ዞረባት፤ነፋስ እንደሚወዘውዘውም ጐጆ ሆነች፣የዐመጿ ሸክም ከባድ ስለ ሆነ ትወድቃለች፤እንደ ገናም አትነሣም።