5. የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣በአዌን ሸለቆ ያለውን ንጉሥ እደመስሳለሁ፤የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”ይላል እግዚአብሔር።
6. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቊጣዬን አልመልስም፤ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣ለኤዶም ሸጣለችና።
7. ምሽጎቿን እንዲበላ፣በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰዳለሁ።
8. በአስቀሎና በትር የያዘውን፣የአሸዶድንም ንጉሥ እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰውእስኪሞት ድረስ፣እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”ይላል ጌታ እግዚአብሔር።