2. ሕዝቦችን በእጅህ አሳደህ አወጣሃቸው፤አባቶቻችንን ግን ተከልሃቸው፤ሕዝቦችን አደቀቅህ፤አባቶቻችንን ግን ነጻ አወጣሃቸው።
3. ምድሪቱን የወረሱት በሰይፋቸው አልነበረም፤ድልንም የተጐናጸፉት በክንዳቸው አይደለም፤አንተ ወደሃቸዋልና ቀኝ እጅህ፣ክንድህና የፊትህ ብርሃን ይህን አደረገ።
4. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ንጉሤ ነህ፤ያዕቆብም ድል እንዲያደርግ የወሰንህ አንተ ነህ።
5. በአንተ ጠላቶቻችን በመጡበት እንዲመለሱ እናደርጋለን፤በስምህም ባላጋራዎቻችንን ከእግራችን በታች እንረግጣለን።
6. በቀስቴ አልተማመንም፤ሰይፌም አያስጥለኝም።
7. አንተ ግን በጠላቶቻችን ላይ ድልን ትሰጠናለህ፤ባላንጣዎቻችንንም ታሳፍራለህ።