መዝሙር 3:1-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶቼ ምንኛ በዙስንቱስ በእኔ ላይ ተነሣ!

2. ብዙዎች ነፍሴን፣ “እግዚአብሔርአይታደግሽም” አሏት። ሴላ

3. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ዙሪያዬንየምትከልል ጋሻ ነህ፤ክብሬና፣ ራሴንም ቀና ቀናየምታደርግ አንተ ነህ።

4. ወደ እግዚአብሔር ድምፄን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ፤እርሱም ከተቀደሰ ተራራው ይመልስልኛል። ሴላ

5. እተኛለሁ፤ አንቀላፋለሁ፤ እግዚአብሔር ደግፎ ይዞኛልና እነቃለሁ።

6. በየአቅጣጫው የከበበኝን፣አእላፍ ሕዝብ አልፈራም።

7. እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ!አምላኬ ሆይ፤ ታደገኝ፤የጠላቶቼን ሁሉ መንጋጋ ትመታለህ፤የክፉዎችንም ጥርስ ትሰባብራለህ።

8. ማዳን የእግዚአብሔር ነው፤በረከትህ በሕዝብህ ላይ ይሁን። ሴላ

መዝሙር 3