መዝሙር 25:1-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ ነፍሴን ወደ አንተ አነሣለሁ፤

2. አምላኬ ሆይ፣ በአንተ እታመናለሁ፤እባክህ አታሳፍረኝ፤ጠላቶቼም አይዘባነኑብኝ።

3. አንተን ተስፋ የሚያደርጉ፣ከቶ አያፍሩም፤ነገር ግን እንዲያው ያለ ምክንያት፣ተንኰለኞች የሆኑ ያፍራሉ።

4. እግዚአብሔር ሆይ፤ አካሄድህን እንዳውቅ አድርገኝ፤መንገድህንም አስተምረኝ።

5. አንተ አዳኜ፣ አምላኬም ነህና፣በእውነትህ ምራኝ፤ አስተምረኝም፤ቀኑን ሙሉ አንተን ተስፋ አድርጌአለሁ።

6. እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህንና ፍቅርህን አስብ፤እነዚህ ከጥንት የነበሩ ናቸውና።

7. የልጅነቴን ኀጢአት፣መተላለፌንም አታስብብኝ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቸርነትህ ብዛት፣እንደ ምሕረትህም መጠን ዐስበኝ።

8. እግዚአብሔር መልካምና ቅን ነው፤ስለዚህ ኀጢአተኞችን በመንገድ ይመራቸዋል።

9. ዝቅ ያሉትን በፍትሕ ይመራቸዋል፤ለትሑታንም መንገዱን ያስተምራቸዋል።

10. ኪዳኑንና ሥርዐቱን ለሚጠብቁ፣ የእግዚአብሔር መንገድ ሁሉ ቸርነትና እውነት ናቸው።

11. እግዚአብሔር ሆይ፤ ኀጢአቴ ታላቅ ነውና፣ስለ ስምህ ይቅር በልልኝ።

12. እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ማን ነው?በተመረጠለት መንገድ ያስተምረዋል።

13. ዘመኑን በተድላ ደስታ ያሳልፋል፤ዘሩም ምድርን ይወርሳል።

14. እግዚአብሔር ምስጢሩን ከሚፈሩት ወዳጆቹ አይሰውርም፤ኪዳኑንም ይገልጥላቸዋል።

መዝሙር 25