መዝሙር 101:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ስለ ምሕረትና ስለ ፍትሕ እዘምራለሁ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ለአንተ በምስጋና እቀኛለሁ።

2. እንከን የማይገኝባትን መንገድ አጥብቄ እይዛለሁ፤አንተ ወደ እኔ የምትመጣው መቼ ነው?በቤቴ ውስጥ፣በንጹሕ ልብ እመላለሳለሁ።

3. በዐይኔ ፊት፣ክፉ ነገር አላኖርም።የከሓዲዎችን ሥራ እጠላለሁ፤ከእኔም ጋር አይጣበቅም።

4. ጠማማ ልብ ከእኔ ይርቃል፤ለክፋትም ዕውቅና አልሰጥም።

መዝሙር 101