መክብብ 7:15-23 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. በዚህ ከንቱ በሆነው ሕይወቴ እነዚህን ሁለቱን ነገሮች አይቻለሁ፤ጻድቅ በጽድቁ ሲጠፋ፣ኀጥእም በክፋቱ ዕድሜው ሲረዝም።

16. እጅግ ጻድቅ፣እጅግም ጠቢብ አትሁን፤ራስህን ለምን ታጠፋለህ?

17. እጅግ ክፉ አትሁን፤ሞኝም አትሁን፤ለምንስ ያለ ቀንህ ትሞታለህ?

18. አንዱን ይዞ ሌላውንም አለመልቀቅ መልካም ነው፤እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውጽንፈኝነትን ያስወግዳል።

19. በአንድ ከተማ ካሉ ዐሥር ገዦች ይልቅ፣ጥበብ ጠቢቡን ሰው ኀያል ታደርገዋለች።

20. ትክክለኛውን ነገር የሚያደርግና ፈጽሞ ኀጢአት የማይሠራ፣ጻድቅ ሰው በምድር ላይ የለም።

21. የሚነገረውን ቃል ሁሉ ለማዳመጥ አትሞክር፤አለበለዚያ አገልጋይህ ሲረግምህ ትሰማ ይሆናል፤

22. ብዙ ጊዜ አንተ ራስህ፣ሌሎችን እንደረገምህ ልብህ ያውቃልና።

23. እኔም ይህን ሁሉ በጥበብ ፈትኜ፣“ጠቢብ ለመሆን ቈርጫለሁ” አልሁ፤ይህ ግን ከእኔ የራቀ ነበር።

መክብብ 7