16. በበጎች ጒረኖ መካከል ለምን ተቀመጥህ?መንጎችን የሚጠራውን ፉጨት ለመስማት ነውን?በሮቤል አውራጃዎች፣ ብዙ የልብምርምር ነበር።
17. ገለዓድ ከዮርዳኖስ ማዶ ተቀመጠ፤ዳን ለምን በመርከብ ውስጥ ዘገየ?አሴር በጠረፍ ቀረ፤በባሕሩ ዳርቻም ተቀመጠ።
18. የዛብሎን ሰዎች ሕይወታቸውን አሳልፈው ሰጡየንፍታሌም ሰዎች እንደዚሁ በምድሪቱ ኰረብታዎች አደረጉ።
19. “ነገሥታት መጡ፤ ተዋጉም፤የከነዓን ነገሥታት፣ በመጊዶ ውሆች”አጠገብ በታዕናክ ተዋጉ፤ብርም ሆነ ሌላ ምርኮ ተሸክመው አልሄዱም።
20. ከሰማያት ከዋክብት ተዋጉ፤በአካሄዳቸውም ሲሣራን ገጠሙት።
21. ጥንታዊው ወንዝ፣ የቂሶን ወንዝ፣የቂሶን ወንዝ ጠርጐ ወሰዳቸው፤ነፍሴ ሆይ፤ በኀይል ገሥግሺ
22. የፈረሶች ኮቴ ድምፅ በኀይል ተሰማ፤ጋለቡ፤ በኀይልም ፈጥነው ጋለቡ።
23. የእግዚአብሔር መልአክ፣ ‘ሜሮዝን ርገሙ፤’‘ሕዝቧንም አብራችሁ ርገሙ፤ከኀያላን ሰልፍ እግዚአብሔርን ለመርዳት፣በእግዚአብሔርም ጐን ለመቆም አልመጡምና’ አለ።
24. ‘የቄናዊው የሔቤር ሚስት ኢያዔል፣ከሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን፤በድንኳን ከሚኖሩ ሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን።
25. ውሃ ለመነ፤ ወተት ሰጠችው፤ለመኳንንት በሚገባ ዕቃ፣ እርጎ አቀረበችለት።
26. እጇዋ ካስማ ያዘ፤ቀኝ እጇም የሠራተኛ መዶሻ ጨበጠ፤ሲሣራን መታችው፤ ራሱንም ተረከከችው፤ክፉኛ ወጋችው፤ ጆሮ ግንዱን በሳችው።
27. በእግሯ ሥር ተደፋ፤ ወደቀ፤በዚያም ተዘረረ፤ በእግሯ ሥር ተደፋ፤ወደቀ፤ በተደፋበት በዚያ ወደቀ፤ሞተም።
28. “የሲሣራ እናት በመስኮት ተመለከተች፤በዐይነ ርግቡ ቀዳዳም ጮኻ ተጣራች፤‘ለምን ሠረገላው ሳይመጣ ዘገየ?የሠረገሎቹስ ድምፅ ለምን ጠፋ?’ አለች።