4. “ኤፍሬም ሆይ፤ ምን ላድርግህ?ይሁዳ ሆይ፤ ምን ላድርግህ?ፍቅራችሁ እንደ ማለዳ ጉም፣እንደሚጠፋም የጧት ጤዛ ነው።
5. ስለዚህ በነቢያቴ ቈራረጥኋችሁ፤በአፌም ቃል ገደልኋችሁ፣ፍርዴም እንደ መብረቅ በላያችሁ አበራ።
6. ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን፣ከሚቃጠልም መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እሻለሁና።
7. እንደ አዳም ቃል ኪዳንን ተላለፉ፤በዚያም ለእኔ ታማኝ አልነበሩም።
8. ገለዓድ በደም የተበከለች፣የክፉዎች ሰዎች ከተማ ናት።
9. ወንበዴዎች ሰውን ለማጥቃት እንደሚያደቡ፣ካህናትም በቡድን እንዲሁ ያደርጋሉ፤በሴኬም መንገድ ላይ ሰዎችን ይገድላሉ፤አሳፋሪም ወንጀል ይፈጽማሉ።
10. በእስራኤል ቤት የሚሰቀጥጥ ነገር አይቻለሁ፤በዚያ ኤፍሬም ዘማዊ ሆነ፤እስራኤልም ረከሰ።
11. “ይሁዳ ሆይ፤ ለአንተም፣መከር ተመድቦብሃል።ሕዝቤን ከምርኮ አገር በመለስሁ ጊዜ፣