ዮሐንስ 11:33-39 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

33. ኢየሱስም እርሷ ስታለቅስ፣ ተከትለዋትም የመጡት አይሁድም ሲያለቅሱ ባየ ጊዜ መንፈሱ በኀዘን ታውኮ፣

34. “የት ነው ያኖራችሁት?” ሲል ጠየቀ።እነርሱም፣ “ጌታ ሆይ፤ መጥተህ እይ” አሉት።

35. ኢየሱስም እንባውን አፈሰሰ።

36. አይሁድም፣ “እንዴት ይወደው እንደ ነበር አያችሁ” አሉ።

37. ከእነርሱ አንዳንዶቹ ግን፣ “የዐይነ ስውሩን ዐይን የከፈተ፣ ይህም ሰው እንዳይሞት ማድረግ አይችልም ነበር?” አሉ።

38. ኢየሱስ ልቡ ዳግመኛ በኀዘን ተነክቶ ወደ መቃብሩ መጣ፤ መቃብሩም በድንጋይ የተገጠመ ዋሻ ነበር፤

39. እርሱም፣ “ድንጋዩን አንሡት” አለ።የሟቹም እኅት ማርታ፣ “ጌታ ሆይ፤ አሁንማ አራት ቀን ስለ ቈየ ይሸታል” አለችው።

ዮሐንስ 11