ኤርምያስ 48:7-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. በድርጊታችሁና በብልጽግናችሁ ስለምትታመኑ፣እናንተም ትማረካላችሁ፣ካሞሽም ከካህናቱና ከመኳንንቱ ጋር፣በምርኮ ይወሰዳል።

8. በእያንዳንዱ ከተማ ላይ አጥፊ ይመጣል፤አንድም ከተማ አያመልጥም። እግዚአብሔር ተናግሮአልና፣ሸለቆው ይጠፋል፤ዐምባውም ይፈርሳል።

9. በራ እንድታመልጥ፣ለሞዓብ ክንፍ ስጧት፤ከተሞቿም ምንም እስከማይኖርባቸው ድረስ፣ባድማ ይሆናሉ።

10. “የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያከናውን ርጉም ይሁን፤ሰይፉን ደም ከማፍሰስ የሚከላከል የተረገመ ይሁን፤

11. “ሞዓብ በአምቡላው ላይ እንዳረፈ የወይን ጠጅ፣ከልጅነት ጀምሮ የተረጋጋ ነበረ፤ከዕቃ ወደ ዕቃ አልተገላበጠም፤በምርኮም አልተወሰደም፤ቃናው እንዳለ ነው፤መዐዛውም አልተለወጠም።

12. ስለዚህ ዕቃውን የሚገለብጡ ሰዎችን፤የምልክበት ጊዜ ይመጣል፤”ይላል እግዚአብሔር።“እነርሱም ይደፉታል፤ዕቃውን ባዶ ያስቀራሉ፤ማንቆርቆሪያዎቹንም ይሰባብራሉ።

13. የእስራኤል ቤት፤በቤቴል ታምኖ እንዳፈረ ሁሉ፣ሞዓብም በካሞሽ ያፍራል።

ኤርምያስ 48