ኤርምያስ 48:41-45 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

41. ከተሞቹ ይወረራሉ፤ምሽጎቹም ይያዛሉ፤በዚያን ቀን የሞዓብ ጦረኞች ልብ፣በምጥ እንደ ተያዘች ሴት ልብ ይሆናል።

42. ሞዓብ እግዚአብሔርን አቃልሎአልና ይጠፋል፤መንግሥትነቱም ይቀራል።

43. የሞዓብ ሕዝብ ሆይ፤ሽብርና ጒድጓድ፣ ወጥመድም ይጠብቅሃል፤”ይላል እግዚአብሔር።

44. “ከሽብር የሚሸሽ ሁሉ፣ጒድጓድ ውስጥ ይገባል፤ከጒድጓዱም የሚወጣ፣በወጥመድ ይያዛል፤በሞዓብ ላይ፣የቅጣቱን ዓመት አመጣለሁና፣”ይላል እግዚአብሔር፤

45. “የሞዓብን ግንባር፣የደንፊዎችን ዐናት የሚያቃጥል፣እሳት ከሐሴቦን፣ነበልባል ከሴዎን ቤት ወጥቶአልና፤ኰብላዮች በሐሴቦን ጥላ ሥር፣ተስፋ ቈርጠው ቆመዋል።

ኤርምያስ 48