1. “ሰው ሚስቱን ቢፈታ፣እርሷም ሄዳ ሌላ ሰው ብታገባ፣ወደ እርሷ ይመለሳልን?ምድሪቱስ ፈጽማ አትረክስምን?አንቺ ግን ከብዙ ወዳጆችሽ ጋር አመንዝረሻል፤ታዲያ አሁን ወደ እኔ መመለስ ትፈልጊያለሽን?”ይላል እግዚአብሔር።
2. “እስቲ ቀና ብለሽ ጭር ያሉትን ኰረብቶች ተመልከቺ፣በርኵሰት ያልተጋደምሽበት ቦታ ይገኛልን?በበረሓ፣ እንደ ተቀመጠ ዘላን ዐረብ፣በየመንገዱ ዳር ተቀምጠሽ ወዳጆችሽን ጠበቅሽ።በዝሙትሽና በክፋትሽ፣ምድሪቱን አረከስሽ።