16. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነዚህ ነቢያት የሚተነብዩላችሁን አትስሙ፤በባዶ ተስፋ ይሞሏችኋል፤ ከእግዚአብሔር አፍ የወጣ ሳይሆን፣ከገዛ ልባቸው የሆነውን ራእይ ይናገራሉ።
17. እኔን ለሚንቁኝ፣‘እግዚአብሔር ሰላም ይሆንላችኋል ብሏል’ ይላሉ፤የልባቸውን እልኸኝነት ለሚከተሉም ሁሉ፣‘ክፉ ነገር አይነካችሁም’ ይሏቸዋል።
18. ቃሉን ለማየትና ለመስማት፣እነማን የእግዚአብሔር ምክር ባለበት ቆመዋል?ቃሉን ያደመጠ፣ የሰማስ ማን ነው?
19. እነሆ፤ የእግዚአብሔር ዐውሎ ነፋስ፣በቍጣ ይነሣል፤ብርቱም ማዕበል፣የክፉዎችን ራስ ይመታል።
20. እግዚአብሔር የልቡን ሐሳብ፣ሙሉ በሙሉ ሳይፈጽም፣ቍጣው እንዲሁ አይመለስም፤በኋለኛው ዘመን፣ይህን በግልጽ ትረዳላችሁ።