ኤርምያስ 22:21-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

21. ተመችቶሽ በነበረ ጊዜ አስጠነቀቅሁሽ፤አንቺ ግን፣ ‘አልሰማም’ አልሽ፤ከትንሽነትሽ ጀምሮ መንገድሽ ይኸው ነበር፤ቃሌንም አልሰማሽም።

22. እረኞችሽ ሁሉ በነፋስ ይወሰዳሉ፤ወዳጆችሽም ተማርከው ይሄዳሉ፤ከክፋትሽም ሁሉ የተነሣ፣ታፍሪያለሽ፤ ትዋረጂያለሽም።

23. አንቺ፣ ‘በሊባኖስ’ ውስጥ የምትኖሪ፣መኖሪያሽን በዝግባ ዛፍ የሠራሽ ሆይ፤ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣መከራ በላይሽ ሲመጣ ጩኸትሽ እንዴት ይሆን!

24. “በሕያውነቴ እምላለሁ”፤ ይላል እግዚአብሔር “የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም ልጅ ኢኮንያን የቀኝ እጄ የቀለበት ማኅተም ብትሆን እንኳ ኖሮ፣ አውልቄ እጥልሃለሁ፤

25. ሕይወትህን ለሚሿት፣ ለምትፈራቸው ለባቢሎናውያንና ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደናፆር አሳልፌ እሰጥሃለሁ።

26. አንተንና የወለደችህን እናትህን ወዳልተወለዳችሁበት ወደ ሌላ አገር ወርውሬ እጥላችኋለሁ፤ በዚያም ትሞታላችሁ።

27. ልትመለሱባት ወደ ምትናፍቋት ምድር ከቶ አትመለሱም።”

ኤርምያስ 22