10. ከእንግዲህ ስለማይመለስ፣የተወለደባትንም ምድር ዳግመኛ ስለማያይ፣ለተማረከው ንጉሥ አምርራችሁ አልቅሱ እንጂ፣ቀድሞ ለሞተው አታልቅሱ፤ አትዘኑም።
11. በአባቱ ምትክ በይሁዳ ላይ ስለ ነገሠው፣ ከዚህ ስፍራ በምርኮ ስለ ተወሰደው፣ ስለ ኢዮስያስ ልጅ ስለ ሰሎ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ “ከእንግዲህ አይመለስም፤
12. ተማርኮ በሄደበት አገር ይሞታል እንጂ ይህቺን ምድር ዳግመኛ አያይም።”
13. “ቤተ መንግሥቱን በግፍ ለሚሠራ፣ሰገነቱንም ፍትሕ በማዛባት ለሚገነባ፣ወገኑን በነጻ ለሚያሠራ፣የድካሙንም ዋጋ ለማይከፍለው፣