11. እነሆ! በአጠገቤ ሲያልፍ አላየውም፤በጐኔም ሲሄድ፣ ልገነዘበው አልችልም።
12. ቢነጥቅ፣ ማን ይከለክለዋል?‘ምን መሥራትህ ነው?’ የሚለውስ፣ ማን ነው?
13. እግዚአብሔር ቍጣውን አይመልስም፤ረዓብን የሚረዱ እንኳ ይሰግዱለታል።
14. “ታዲያ፣ ከእርሱ ጋር እሟገት ዘንድ፣ልከራከረውም ቃላት እመርጥ ዘንድ፣ እንዴት እችላለሁ?
15. ጻድቅ ብሆንም እንኳ፣ ልመልስለት አልችልም፤ዳኛዬን ምሕረት ከመለመን ሌላ ላደርግ የምችለው የለም።
16. ጠርቼው ‘አቤት!’ ቢለኝም፣ያዳምጠኛል ብዬ አላምንም።
17. በዐውሎ ነፋስ ይሰብረኛል፤ቍስሌንም ያለ ምክንያት ያበዛል፤
18. ምሬትን አጠገበኝ እንጂ፣ለመተንፈስ እንኳ ፋታ አልሰጠኝም።
19. የኀይል ነገር ከተነሣ፣ እርሱ ኀያል ነው!የፍትሕም ነገር ከተነሣ፣ መጥሪያ ሊሰጠው የሚችል ማን ነው?
20. ንጹሕ ብሆን እንኳ፣ አንደበቴ ይፈርድብኛል፣እንከን የለሽ እንኳ ብሆን፣ በደለኛ ያደርገኛል።