6. ያን የጩኸት ድምፅ ከከተማው ስሙ!ያን ጫጫታ ከቤተ መቅደሱ ስሙ!ይኸውም የእግዚአብሔር ድምፅ ነው፤ለጠላቶቹም የሚገባቸውን ሁሉ ይከፍላቸዋል።
7. “ከማማጧ በፊት፣ትወልዳለች፤በምጥ ጣር ከመያዟ በፊት፣ወንድ ልጅ ትገላገላለች።
8. እንዲህ ያለ ነገር ማን ሰምቶ ያውቃል?እንዲህ ያለ ነገርስ ማን አይቶ ያውቃል?አገር በአንድ ጀምበር ይፈጠራልን?ወይስ ሕዝብ በቅጽበት ይገኛል?ጽዮንን ምጥ ገና ሲጀምራት፣ልጆቿን ወዲያውኑ ትወልዳለች።
9. ሊወለድ የተቃረበውን፣እንዳይወለድ አደርጋለሁን?” ይላል እግዚአብሔር።“በሚገላገሉበት ጊዜስ፣ማሕፀን እዘጋለሁን?” ይላል አምላክሽ።