4. ይህን የሠራና ያደረገ፣ትውልድን ከጥንት የጠራ ማን ነው?እኔ እግዚአብሔር ከፊተኛው፣ከኋለኛውም ጋር፤ እኔው ነኝ።”
5. ደሴቶች አይተው ፈሩ፤የምድር ዳርቾች ደነገጡ፤ቀረቡ፤ ወደ ፊትም መጡ።
6. እያንዳንዱ ይረዳዳል፤ወንድሙንም፣ “አይዞህ” ይለዋል።
7. ባለጅ የወርቅ አንጥረኛውን ያበረታታዋል፤በመዶሻ የሚያሳሳውም፣በመስፍ ላይ የሚቀጠቅጠውን ያነቃቃዋል፤ስለ ብየዳም ሥራው፣ “መልካም ነው” ይለዋል፤የጣዖቱ ምስል እንዳይወድቅም በምስማር ያጣብቀዋል።