26. እኛ እናውቅ ዘንድ ይህን ከመጀመሪያው የተናገረ፣‘እርሱ ትክክል ነው’ እንልም ዘንድ ቀድሞ የተናገረ ማነው?ማንም አልተናገረም፤ቀደም ብሎ የተናገረ የለም፤ቃላችሁንም የሰማ የለም።
27. በመጀመሪያ፣ ‘እነሆ፤ ተመልከቺአቸ’ብዬ ለጽዮን የተናገርሁ እኔ ነበርሁ፤ለኢየሩሳሌምምየምሥራች ነጋሪን ሰጥቻለሁ።
28. ተመለከትሁ ማንም አልነበረም፤ከመካከላቸው አማካሪ የለም፤ስጠይቅም መልስ የሚሰጥ የለም።
29. እነሆ፤ ሁሉም ከንቱ ናቸው፤ሥራቸውም መና ነው፤ምስሎቻቸውም ባዶ ነፋስ ናቸው።