ኢሳይያስ 40:23-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

23. አለቆችን ኢምንት፣የዚህን ዓለም ገዦች እንዳልነበሩ ያደርጋቸዋል።

24. ተተክለው ምንም ያህል ሳይቈዩ፣ተዘርተው ምንም ያህል ሳይሰነብቱ፣ገና ሥር መስደድ ሳይጀምሩአነፈሰባቸው፤ እነርሱም ደረቁ፤ዐውሎ ነፋስም እንደ ገለባ ጠራርጎ ወሰዳቸው።

25. ቅዱሱ፣ “ከማን ጋር ታወዳድሩኛላችሁ?የሚስተካከለኝስ ማን አለ?” ይላል።

26. ዐይናችሁን አንሡ፤ ወደ ሰማይ ተመልከቱ፤እነዚህን ሁሉ የፈጠረ ማን ነው?የከዋክብትን ሰራዊት አንድ በአንድ የሚያወጣቸው፣በየስማቸው የሚጠራቸው እርሱ ነው።ከኀይሉ ታላቅነትና ከችሎታው ብርታት የተነሣ፣አንዳቸውም አይጠፉም።

27. ያዕቆብ ሆይ፤ ለምን እንዲህ ትላለህ?እስራኤል ሆይ፤ ለምን እንዲህ ትናገራለህ?“መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች፤ፍርዴም በአምላኬ ቸል ተብላለች” ለምን ትላለህ?

ኢሳይያስ 40