18. በዚያም ቀን ጌታ የክብር ጌጣቸውን ይነጥቃቸዋል፤ የእግር አንባሩን፣ የጠጒር ጌጡን፣ የጨረቃ ቅርጽ ያለውን የዐንገት ጌጥ፣
19. የጆሮ ጒትቻውን፣ የእጅ አንባሩን፣ የፊት መሸፈኛውን፣
20. የራስ መሸፈኛውን፣ ዐልቦውን፣ ሻሹን፣ የሽቶ ብልቃጡን፣ አሸንክታቡን፣
21. የጣት ቀለበቶችንና የአፍንጫ ቀለበቶችን፣
22. ያማረውን ቀሚስ፣ የውስጥ ልብሱን፣ ካባውን፣ የእጅ ቦርሳውን፣
23. መስታወቱን፣ ከጥሩ በፍታ የተሠራውን ልብስ፣ የራስ ጌጡን፣ ዐይነ ርግቡን ሁሉ ይነጥቃቸዋል።
24. በሽቶ ፈንታ ግማት፣በሻሽ ፈንታ ገመድ፣አምሮ በተሠራ ጠጒር ፈንታ ቡሀነት፣ባማረ ልብስ ፈንታ ማቅ፣በውበትም ፈንታ ጠባሳ ይሆናል።