ኢሳይያስ 22:16-25 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. ‘እዚህ ምን ታደርጋለህ?በዚህ ስፍራ ለራስህ መቃብርን እንድ ታዘጋጅ፣በከፍታውም ላይ መቀበሪያህን እንድ ትወቅር፣ሬሳህ የሚያርፍበትንም ዐለት እንድ ትጠርብ ማን ፈቀደልህ?’

17. አንተ ኀያል ሰው ሆይ፤ ተጠንቀቅ፤ እግዚአብሔር አጥብቆ ሊይዝህ፣ በእጆቹም ጨብጦ ሊወረውርህ ነው።

18. አዙሮ አዙሮ እንደ ሩር አጡዞ፣ወደ ሰፊ አገር ይወነጭፍሃል፤አንተ የጌታህ ቤት ዕፍረበዚያ ትሞታለህ፤የክብር ሠረገሎችህም እዚያ ይቀራሉ።

19. ከማዕረግህ አወርድሃለሁ፤ከኀላፊነትህም ትባረራለህ።

20. “በዚያን ቀን አገልጋዬን፣ የኬልቅያስን ልጅ ኤልያቄምን እጠራለሁ፤

21. መጐናጸፊያህን አለብሰዋለሁ፤ መታጠቂያህን አስታጥቀዋለሁ፤ ሥልጣንህንም አስረክበዋለሁ። እርሱም በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ፣ ለይሁዳም ቤት አባት ይሆናል።

22. የዳዊትን ቤት መክፈቻ በጫንቃው ላይ አደርጋለሁ፤ እርሱ የሚከፍተውን ማንም አይዘጋም፤ የሚዘጋውንም ማንም አይከፍትም።

23. በአስተማማኝ ስፍራ እንደ ካስማ እተክለዋለሁ፤ ለአባቱም ቤት የክብር ዙፋን ይሆናል።

24. የቤተ ሰቡ ክብር፣ ልጅና የልጅ ልጅ፣ እንዲሁም ከማሰሮ ጀምሮ እስከ ጋን ድረስ ያለ የቤት ዕቃ ሁሉ በርሱ ላይ ይንጠለጠላል።

25. “በዚያ ቀን” ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣ “በአስተማማኝ ስፍራ የተተከለ ካስማ ይነቀላል፤ ተሰብሮም ይወድቃል፤ በእርሱም ላይ የተንጠለጠለው ሸክም ወድቆ ይከሰከሳል፤” እግዚአብሔር ይህን ተናግሮአልና።

ኢሳይያስ 22