31. እግዚአብሔር ሰውን፣ለዘላለም አይጥልምና፤
32. መከራን ቢያመጣ እንኳ ይራራል፤ታላቅ ፍቅሩ አይለወጥምና
33. ሆን ብሎ ችግርን፣ወይም መከራን በሰው ልጆች ላይ አያመጣምና።
34. የምድሪቱ እስረኞች ሁሉ፣በእግር ሲረገጡ፣
35. በልዑል ፊት፣ሰው መብቱ ሲነፈገው፣
36. ሰው ፍትሕ ሲጓደልበት፣ጌታ እንዲህ ዐይነቱን ነገር አያይምን?
37. እግዚአብሔር ካላዘዘ በቀር፤ተናግሮ መፈጸም የሚችል ማን ነው?