10. አሸምቆ እንደ ተኛ ድብ፣እንደ አደባም አንበሳ፣
11. ከመንገድ ጐትቶ አስወጣኝ፤ ቈራረጠኝም፤ያለ ረዳትም ተወኝ።
12. ቀስቱን ገተረ፤ለፍላጻዎቹም ዒላማ አደረገኝ።
13. ፍላጻዎችን ከሰገባው አውጥቶ፣ልቤን ወጋው።
14. ለሕዝቤ ሁሉ ማላገጫ ሆንሁኝ፤ቀኑን ሙሉ በመሣለቅ ያዜሙብኛል።
15. መራራ ሥር አበላኝ፤ሐሞትም አጠገበኝ።
16. ጥርሴን በድንጋይ ሰበረ፤በትቢያ ውስጥ ረጋገጠኝ።
17. ነፍሴ ሰላምን አጣች፤ደስታ ምን እንደሆነ ረሳሁ።
18. ስለዚህ፣ “ክብሬ፣ ከእግዚአብሔርም ተስፋ ያደረግሁት ሁሉ ሄዶአል” አልሁ።
19. የጭንቀቴንና የመንከራተቴን፣ምሬትንና ሐሞትን አስባለሁ።