9. ሽቱና ዕጣን ልብን ደስ ያሰኛሉ፤የወዳጅ ማስደሰትም ከቅን ምክሩ ይመነጫል።
10. የራስህንም ሆነ የአባትህን ወዳጅ አትተው፤መከራ በሚያጋጥምህ ጊዜ ወደ ወንድምህ ቤት አትሂድ፤ሩቅ ካለ ወንድም ቅርብ ያለ ጎረቤት ይሻላል።
11. ልጄ ሆይ፤ ጠቢብ ሁን፤ ልቤን ደስ አሰኘው፤ለሚንቁኝ ሁሉ መልስ መስጠት እችል ዘንድ።
12. ጥንቁቅ አደጋን አይቶ ይሸሸጋል፤ማስተዋል የጐደለው ግን ወደዚያው ይሄዳል፤ ይጐዳልም።