መዝሙር 60:3-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ለሕዝብህ አበሳውን አሳየኸው፤ናላ የሚያዞር የወይን ጠጅ እንድንጠጣም ሰጠኸን።

4. ነገር ግን ከቀስት እንዲያመልጡ፣ለሚፈሩህ ምልክት አቆምህላቸው። ሴላ

5. ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣በቀኝ እጅህ ርዳን፤ መልስም ስጠን።

6. እግዚአብሔር ከመቅደሱ እንዲህ ሲል ተናገረ፤“ደስ እያለኝ የሴኬምን ምድር እሸነሽናለሁ፤የሱኮትን ሸለቆ አከፋፍላለሁ።

7. ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤ይሁዳም በትረ መንግሥቴ ነው።

8. ሞዓብ የመታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤በፍልስጥኤም ላይ በድል እልል እላለሁ።”

9. ወደ ተመሸገው ከተማ ማን ያመጣኛል?ማንስ ወደ ኤዶምያስ ይመራኛል?

መዝሙር 60