19. ወደ ሰፊ ስፍራ አወጣኝ፤ደስ ተሰኝቶብኛልና አዳነኝ።
20. እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ መልሶልኛል፤እንደ እጄ ንጽሕናም ከፍሎኛል፤
21. የእግዚአብሔርን መንገድ ጠብቄአለሁና፤አምላኬንም በመተው ክፉ አላደረግሁም።
22. ሕጎቹ ሁሉ በፊቴ ናቸው፤ሥርዐቱን ከፊቴ አላራቅሁም።
23. በፊቱ ነቀፋ አልነበረብኝም፤ራሴንም ከኀጢአት ጠብቄአለሁ።
24. እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ መጠን፣በፊቱም እንደ እጄም ንጽሕና ከፍሎኛል።
25. ከታማኙ ጋር ታማኝ ትሆናለህ፤እንከን ከሌለበት ጋር ያለ እንከን ትሆናለህ፤