1. ሃሌ ሉያ። እግዚአብሔርን ከሰማያት አመስግኑት፤በላይ በአርያም አመስግኑት።
2. መላእክቱ ሁሉ አመስግኑት፤ሰራዊቱ ሁሉ አመስግኑት፤
3. ፀሓይና ጨረቃ አመስግኑት፤የምታበሩ ከዋክብት ሁሉ አመስግኑት።
4. ሰማየ ሰማያት አመስግኑት፤ከሰማያትም በላይ ያላችሁ ውሆች አወድሱት።
5. እርሱ ስላዘዘ ተፈጥረዋልና፣ የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑት።
6. ከዘላለም እስከ ዘላለም አጸናቸው፤የማይሻርም ሕግ ደነገገላቸው።