መዝሙር 139:9-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. በንጋት ክንፍ ተነሥቼ ብበር፣እስከ ባሕሩ ዳርቻ መጨረሻ ብሄድ፣

10. በዚያም ቢሆን እጅህ ትመራኛለች፤ቀኝ እጅህም አጥብቃ ትይዘኛለች።

11. እኔም፣ “ጨለማው በርግጥ ይሰውረኛል፤በዙሪያዬ ያለውም ብርሃን ሌሊት ይሆናል” ብል፣

12. ጨለማ የአንተን ዐይን አይዝም፤ሌሊቱም እንደ ቀን ያበራል፤ጨለማም ብርሃንም ለአንተ አንድ ናቸውና።

13. አንተ ውስጣዊ ሰውነቴን ፈጥረሃልና፤በእናቴም ማሕፀን ውስጥ አበጃጅተህ ሠራኸኝ።

14. ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤ሥራህ ድንቅ ነው፤ነፍሴም ይህን በውል ተረድታለች።

15. እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ፣ዐጥንቶቼ ከአንተ አልተደበቁም፤በምድር ጥልቀት ውስጥ በጥበብ በተሠራሁ ጊዜ፣

መዝሙር 139