መዝሙር 109:27-30 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

27. እግዚአብሔር ሆይ፤ እጅህ ይህን እንዳደረገች፣አንተም ይህን እንደ ፈጸምህ ይወቁ።

28. እነርሱ ይራገማሉ፤ አንተ ግን ትባርካለህ፤በሚነሡበት ጊዜ ይዋረዳሉ፤ባሪያህ ግን ሐሤት ያደርጋል።

29. የሚወነጅሉኝ ውርደትን ይከናነቡ፤ዕፍረትንም እንደ ሸማ ይልበሱ።

30. እግዚአብሔርን በአንደበቴ እጅግ አመሰግናለሁ፤በታላቅ ሕዝብም መካከል አወድሰዋለሁ።

መዝሙር 109