19. ገላውን እንደሚሸፍንበት ልብስ፣ዘወትር እንደሚታጠቀውም መቀነት ትሁነው።
20. እግዚአብሔር ለሚወነጅሉኝ ሰዎች፣በነፍሴም ላይ ክፉ ለሚናገሩ የሚከፍላቸው ይኸው ይሁን።
21. አንተ ግን ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ስለ ስምህ በበጎ ተመልከተኝ፤ምሕረትህም መልካም ናትና አድነኝ።
22. እኔ ድኻና ችግረኛ ነኝና፤ልቤም በውስጤ ቈስሎአልና።
23. እንደ ምሽት ጥላ ከእይታ ተሰውሬአለሁ፤እንደ አንበጣም ረግፌአለሁ።
24. ከጾም የተነሣ ጒልበቴ ዛለ፤ሰውነቴም ከስቶ ዐመድ ለበሰ።
25. ለመሣለቂያ ሆንሁላቸው፤ሲያዩኝም ራሳቸውን ይነቀንቃሉ።