መክብብ 5:7-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ብዙ ሕልምና ብዙ ቃል ከንቱ ነው፤ ስለዚህ እግዚአብሔርን ፍራ።

8. በአገር ውስጥ ድኻ ተጨቍኖ፣ ፍትሕ ተጓድሎ፣ መብትም ተረግጦ ብታይ፣ እንደነዚህ ባሉ ነገሮች አትደነቅ፤ ምክንያቱም አንዱን አለቃ የበላዩ ይመለከተዋል፤ በእነዚህ በሁለቱም ላይ ሌሎች ከፍ ያሉ አሉ።

9. ከምድሩ የሚገኘው ትርፍ ለሁሉም ነው፤ ንጉሡም ራሱ የሚጠቀመው ከዕርሻ ነው።

10. ገንዘብን የሚወድ፣ ገንዘብ አይበቃውም፤ብልጽግናም የሚወድ፣ በትርፉ አይረካም፤ይህም ከንቱ ነው።

11. ሀብት በበዛ ቊጥር፣ተጠቃሚውም ይበዛል፤በዐይኑ ብቻ ከማየት በቀርታዲያ፣ ለባለቤቱ ምን ይጠቅመዋል?

12. ጥቂትም ይሁን ብዙ ቢበላ፣የሠራተኛ እንቅልፍ ጣፋጭ ነው፤የሀብታም ሰው ብልጽግና ግንእንቅልፍ ይነሣዋል።

መክብብ 5