21. ጥንታዊው ወንዝ፣ የቂሶን ወንዝ፣የቂሶን ወንዝ ጠርጐ ወሰዳቸው፤ነፍሴ ሆይ፤ በኀይል ገሥግሺ
22. የፈረሶች ኮቴ ድምፅ በኀይል ተሰማ፤ጋለቡ፤ በኀይልም ፈጥነው ጋለቡ።
23. የእግዚአብሔር መልአክ፣ ‘ሜሮዝን ርገሙ፤’‘ሕዝቧንም አብራችሁ ርገሙ፤ከኀያላን ሰልፍ እግዚአብሔርን ለመርዳት፣በእግዚአብሔርም ጐን ለመቆም አልመጡምና’ አለ።
24. ‘የቄናዊው የሔቤር ሚስት ኢያዔል፣ከሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን፤በድንኳን ከሚኖሩ ሴቶች ሁሉ የተባረከች ትሁን።
25. ውሃ ለመነ፤ ወተት ሰጠችው፤ለመኳንንት በሚገባ ዕቃ፣ እርጎ አቀረበችለት።