ሕዝቅኤል 31:3-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ለጫካው ጥላ የሆኑ የሚያማምሩ ቅርንጫፎች የነበሩትን፣እጅግ መለሎ ሆኖ፣ጫፉ ሰማይ የደረሰውን፣የሊባኖስን ዝግባ አሦርን ተመልከት።

4. ውሆች አበቀሉት፤ጥልቅ ምንጮች አሳደጉት፤ጅረቶቻቸው ፈሰሱ፤የሥሮቹንም ዙሪያ ሁሉ አረሰረሱ፤በመስኩ ላይ ወዳሉት ዛፎች ሁሉ፣መስኖዎቻቸውን ለቀቁት።

5. ስለዚህ በደን ካሉት ዛፎች ሁሉ፣እጅግ ከፍ አለ፤ቅርንጫፎቹ በዙ፤ቀንበጦቹ ረዘሙ፤ከውሃውም ብዛት የተነሣ ተስፋፉ።

6. የሰማይ ወፎች ሁሉ፣በቅርንጫፎቹ ላይ ጐጆአቸውን ሠሩ፤የምድር አራዊት ሁሉ፣ከቅርንጫፎቹ ሥር ግልገሎቻቸውን ወለዱ።ታላላቅ መንግሥታትም ሁሉ፣ከጥላው ሥር ኖሩ።

7. ከተንሰራፉት ቅርንጫፎቹ ጋር፣ውበቱ ግሩም ነበር፤ብዙ ውሃ ወዳለበት፣ሥሮቹ ጠልቀው ነበርና።

ሕዝቅኤል 31