ሆሴዕ 9:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እስራኤል ሆይ፤ ደስ አይበልሽ፤እንደ ሌሎችም ሕዝቦች ሐሤት አታድርጊ፤ለአምላክሽ ታማኝ አልሆንሽምና፤በየእህል ዐውድማውም ላይ፣ለጋለሞታ የሚከፈለውን ዋጋ ወደሻል።

2. የእህል አውድማዎችና የወይን መጭመቂያዎች ሕዝቡን አይመግቡም፤አዲሱም የወይን ጠጅ ይጐድልባቸዋል።

3. በእግዚአብሔር ምድር አይቀመጡም፤ኤፍሬም ወደ ግብፅ ይመለሳል፤የረከሰውንም ምግብ በአሦር ይበላል።

4. የወይን ጠጅን ቍርባን ለእግዚአብሔር አያፈሱም፤መሥዋዕታቸውም ደስ አያሰኘውም፤እንዲህ ዐይነቱ መሥዋዕት ለእነርሱ የሐዘንተኞች እንጀራ ይሆንባቸዋል፤የሚበሉትም ሁሉ ይረክሳሉ።ይህ ምግብ ለገዛ ራሳቸው ይሆናል፤ወደ እግዚአብሔርም ቤተ መቅደስ አይገባም።

ሆሴዕ 9