1. እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤
2. “ስጦታ እንዲያመጡልኝ ለእስራኤላውያን ንገራቸው። ይሰጥ ዘንድ ልቡ ካነሣሣው ከእያንዳንዱ ሰው ስጦታን ተቀበልልኝ።
3. ከእነርሱ የምትቀበላቸው ስጦታዎች እነዚህ ናቸው፦ ወርቅ፣ ብርና፣ ነሐስ፣
4. ሰማያዊ፣ ሐምራዊ፣ ቀይ ማግና የበፍታ ድር ልብስ፣ የፍየል ጠጒር፣
5. ቀይ የተነከረ የአውራ በግ ቆዳ፣ የለፋ ቆዳ፣ የግራር ዕንጨት፣
6. የመብራት ወይራ ዘይት፣ ለቅብዓ ዘይቱና ጣፋጭ መዓዛ ላለው ዕጣን የሚሆኑ ቅመሞች፣