27. ባሪያዎችህን አብርሃምን፣ ይስሐቅንና ያዕቆብን አስብ፤ የዚህን ሕዝብ ልበ ደንዳናነት፣ ክፋትና ኀጢአት አትመልከት።
28. አለበለዚያ እኛን ካመጣህበት ምድር ያሉ ሰዎች “እግዚአብሔር (ያህዌ) ተስፋ ወደ ሰጣቸው ምድር ሊያገባቸው ስላልቻለና ስለጠላቸው፤ ‘በምድረ በዳ ሊገድላቸው አወጣቸው ይላሉ።’
29. ነገር ግን እነርሱ በታላቅ ኀይልህና በተዘረጋች ክንድህ ያወጣሃቸው ሕዝብህና ርስትህ ናቸው።”