25. የደጃፍህ መቀርቀሪያ ብረትና ናስ ይሆናል፤ኀይልህም በዘመንህ ሁሉ ይኖራል።
26. አንተን ለመርዳት በሰማያት ላይ፣በግርማው በደመናትም የሚገሠግሥ፣እንደ ይሽሩን አምላክ (ኤሎሂም) ያለ ማንም የለም።
27. ዘላለማዊ አምላክ (ኤሎሂም) መኖርያህ ነው፤የዘላለም ክንዶቹም ከሥርህ ናቸው፤‘እርሱን አጥፋው!’ በማለት፣ጠላትህን ከፊትህ ያስወግደዋል።
28. ስለዚህ እስራኤል ብቻውን በሰላም ይኖራል፤የሰማያት ጠል በሚወርድበት፣እህልና የወይን ጠጅ ባለበት ምድር፣የያዕቆብ ምንጭ የሚነካው የለም።