21. አምላክ ባልሆነው አስቀኑኝ፤በከንቱ ጣዖቶቻቸው አስቈጡኝ።እኔም ሕዝብ ባልሆነው አስቀናቸዋለሁ።በማያስተውልም ሕዝብ አስቈጣቸዋለሁ።
22. በቊጣዬ እሳት ተቀጣጥሎአልና፤እርሱ እስከ ሲኦል ዘልቆ ይነዳል።ምድርን እስከ ሰብሏ ይበላል፤የተራሮችንም መሠረት ያቀጣጥላል።
23. “በመዓት ላይ መዓት አመጣባቸዋለሁ።ፍላጻዬንም በእነርሱ ላይ እጨርሳለሁ።
24. የሚያጠፋ ራብ፣ በልቶ የሚጨርስ ቸነፈርና ከባድመቅሠፍት እሰድባቸዋለሁ፤የአራዊትን ሹል ጥርስ፣ በምድር የሚሳብ የእባብ መርዝምእሰድባቸዋለሁ።
25. ሰይፍ መንገድ ላይ ያስቀራቸዋል፤ቤታቸውም ውስጥ ድንጋጤ ይነግሣል፤ጐልማሳውና ልጃገረዷ፣ሕፃኑና ሽማግሌው ይጠፋሉ።
26. እበትናቸዋለሁ፤ ከሰዎችም መካከል መታሰቢያቸውንአጠፋለሁ አልሁ፤
27. ነገር ግን ጠላቶቻቸው እንዳይታበዩ፣‘ድል ያደረገችው እጃችን እንጂ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን ሁሉ አላደረገም እንዳይሉ፣’ ”የጠላትን መነሣሣት ሠጋሁ።
28. አእምሮ የጐደላቸው፣ማስተዋልም የሌላቸው ናቸው።
29. አስተዋዮች ቢሆኑ ኖሮ ይህን በተገነዘቡ፣መጨረሻቸውም ምን እንደሚሆን ባስተዋሉ ነበር።
30. መጠጊያ ዐለታቸው ካልሸጣቸው፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ካልተዋቸው በቀር፣አንድ ሰው እንዴት ሺሁን ያሳድዳል?ሁለቱስ እንዴት ዐሥር ሺሁን እንዲሸሹ ያደርጋሉ?
31. የእነርሱ መጠጊያ ዐለት እንደ እኛ መጠጊያዐለት አይደለምና፤ ጠላቶቻችንም እንኳ ይህን አይክዱም።
32. ወይናቸው ከሰዶም ወይን፣ከገሞራም እርሻ ይመጣል፤የወይናቸው ፍሬ በመርዝ፣ዘለላቸውም በምሬት የተሞላ ነው።
33. ወይናቸው የእባብ መርዝ፣የመራዥ እባብም መርዝ ነው።
34. “ይህ በእኔ ዘንድ ተጠብቆ ያለ፣በመዝገቤስ የታተመ አይደለምን?
35. በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ፤ጊዜው ሲደርስ እግራቸው ይሰናከላል፤የመጥፊያቸው ቀን ቀርቦአል፤የሚመጣባቸውም ፍርድ ፈጥኖባቸዋል።”
36. ኀይላቸው መድከሙን፣ባሪያም ሆነ ነጻ ሰው አለመቅረቱን በሚያይበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሕዝቡ ይፈርዳል፤ለአገልጋዮቹም ይራራል።
37. እንዲህም ይላል፤ “መጠጊያ ዐለት የሆኗቸው፣እነዚያ አማልክታቸው የት አሉ?
38. የመሥዋዕታቸውን ስብ የበሉ፣የመጠጥ ቊርባናቸውንም የወይን ጠጅ የጠጡ አማልክት ወዴት ናቸው?እስቲ ይነሡና ይርዷችሁ!እስቲ መጠለያ ይስጧችሁ!
39. “እኔ ራሴ እርሱ እንደሆንሁ እዩ፤ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም፤እገድላለሁ፤ አድናለሁም፤አቈስላለሁ፤ እፈውሳለሁም፤ከእጄም የሚያስጥል ማንም የለም።
40. እጄን ወደ ሰማይ አነሣለሁ፤ለዘላለምም ሕያው እንደሆንሁ እናገራለሁ፤
41. የሚያብረቀርቅ ሰይፌን ስዬ፣እጄ ለፍርድ ስትይዘው፣ባላጋራዎቼን እበቀላቸዋለሁ፤የሚጠሉኝንም እንደ ሥራቸው እከፍላቸዋለሁ።